Wednesday, 22 November 2023 20:21

እነሆ ድልድዩን !

Written by 
Rate this item
(0 votes)

እነሆ ድልድዩን !
ይህንን መጽሐፍ አንብቤ እንዳጠናቀቅኩ በሃሳቤ " የሰው ልጅ ስልጣን ላይ ሆኖ ባበበበት ወቅት (በተወደደበት ጊዜ ) ያቺ ጊዜ ሳታልፍ ለተተኪው ትውልድ ስልጣኑን ቢያስረክብ በታሪክ ውስጥ ዘላለማዊ ይሆናል ። ታላቅነቱንም ምንጊዜም ትውልድ ይመሰክርለታል። እርሱም ካደለው ይህንን በህይወት ቆሞ ያያል ።" በማለት አብሰለሰልኩ ።
የመጽሐፉ ርእስ " ዘውድ ያልደፋው ንጉሥ " ደራሲው ደረጀ ተክሌ ወልደ ማሪያም ሲሆን በ452 ገጽ ተጠርዞ  በ500 ብር ገበያ ላይ ውሏል።
ባለታሪኩ ጸሐፌ ትእዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ ናቸው ። ከ1893 - 1968 ዓም እዚህ ምድር ላይ ያኖረዋል ።በአፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ከፍተኛ ባለስልጣን ነበሩ ። እኝህ ድንቅ ሰው ምን እንደከወኑ ደረጄ ማለፊያ በሆነ ትረካ ያወጋናል እና መጽሐፉን ገዝቶም ሆነ ፈልጎ ማንበቡን ለእናንተ ልተው ። እኔ ስለጀግናው ቀደም ብሎ መረጃ ቢኖረኝም ደረጀ መረጃዬን ጥብስቅ ስላደሰገልኝ ላመሰግነው እወዳለሁ ። ጸሐፌ ትእዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ ለጃንሆይ ምን ብለዋቸው ነው ከላይ በጥቅስ ያስቀመጥኩትን አባባል ያልኩት ? ጸሐፌ ትእዛዝ የጥንቱን ትውልድ ከአዲስ ትውልድ ያገናኙ ድልድይ ነኝ ይላሉ ። ... የእንግሊዝን መንግስት የኢትዮጵያ ሞግዚትነት አምክነው አገራችንን ነፃነቷን እንድትጎናጸፍ ካደረጉ አርቆ አሳቢዎች መካከል አውራውም ናቸው ። ...
መልሱን ከመጽሐፉ ታገኙታላችሁ ።
ሰላም በምድራችን ላይ ይስፈን !

Read 1393 times