Tuesday, 17 December 2024 21:01

ሁላችሁም በአክብሮት ተጋብዛችኋል! #photographexhibition

Written by 
Rate this item
(2 votes)

የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወ/ሥላሴ የሥነ-ጥበባት ማዕከል ከአዲስ አበባ ፎቶግራፍ ባለሙያዎች ማኅበር ጋር በመተባበር የፎቶግራፍ አውደርዕይ አዘጋጅቷል፡፡
በዚህ አውደርዕይ ታዋቂ ባለሙያዎች አንቶኒዮ ፍዮሬንቴ፣ ሙሉጌታ አየነ፣ ማኅደር ኃይለሥላሴ፣ ናሆም ተስፋዬና ሚካኤል ጸጋዬ ሥራዎቻቸውን ያቀርባሉ፡፡
አውደርዕዩ ቅዳሜ ታህሳስ 12 2017 ዓ.ም 10፡00 ላይ በአካዳሚው ሙዚየም በይፋ ይከፈታል፡፡ መግቢያው በነጻ ሲኾን እንዲታደሙ በአክብሮት ተጋብዘዋል፡፡
የዝግጅቱ ቦታ:- በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ የሥነ-ጥበባት ማዕከል፡፡
ከፒያሳ ወደ ውንጌት መስመር በሚወስደው ጎዳና - ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል አካባቢ -
በተለምዶ ወረዳ ስምንት ተብሎ በሚጠራው ቀጭን መንገድ 500 ሜትር ገባ ብሎ
ወይንም ንግድ ባንክ ጉለሌ ቅርንጫፍ በኩል

Read 1014 times