በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት አካባቢ ያሉትን ጊዜያቶች የሚዳስሰው የአቶ በረከት መጽሐፍ፤ ከ97 አገራዊ ምርጫ በፊት እና በኋላ የነበሩትን ሂደቶችም ያካትታል፡፡ መጽሐፉ 350 ገፆች እንዳሉት ለማወቅ ተችሏል፡፡ በአገሪቱ ፖለቲካ ላይ ቀውስ ያስከተለውን ምርጫ 97 በተመለከተ ከተቃዋሚዎች ጎራ ጥቂት የማይባሉ መጻሕፍት መውጣታቸው የሚታወስ ሲሆን ከገዢው ፓርቲ ወገን ምርጫውን በተመለከተ ሲጽፉ አቶ በረከት ስምዖን የመጀመሪያው ናቸው፡፡