ትርጉም እያዛባ፣ቃል እያናናቀ፣
ፍቺ እያጣረሰ፤
ከበሽታ ሁሉ የደሃ ኩርፊያ ነው
ሃገር ያፈረሰ።
እናንተ ብልሆች!
ተስፋ−ተስፋ የሚሸት እቅድ ስታቅዱ፣
ንቁ−ፍኩ እንዲሆን የለውጥ መንገዱ፤
‘ካኮረፈ ደሃ’ ሃሳብ አትውሰዱ!
የለቅሶ ቤት አዝማች
ተዝካር፣
እዝን፣
ድንኳን፣
ንፍሮ፣
ሰልስት፤
12፣ 40፣ 80፣ ሙት−ዓመት፤
“ጐጂ ነው!” አትበሉን አቦ እናልቅስበት!
እናውቃለን እኮ!
አዛኞች፣ አጽናኞች በሞሉባት አምባ፤
‘ግማሽ ሳቅ’ ማለት ነው ሁሉ ያየው ዕንባ።