Monday, 16 September 2013 08:20

“17ቱ የስኬታማ ህይወት ሚስጥራት” እየተነበበ ነው

Written by 
Rate this item
(17 votes)

በናፖሊዮን ሂል የተፃፈው “The 17 principles of success” የተሰኘ የስኬት መርሆዎችን የያዘ መፅሃፍ “17ቱ የስኬታማ ህይወት ምስጢራት” በሚል በፋንታሁን ሃይሌ ተርጓሚነትና በእስክንድር ስዩም አርታኢነት ለንባብ በቅቷል፡፡
ተርጓሚው በመፅሃፉ መቅድም ላይ ባሰፈረው መልዕክት “የዚህ መፅሃፍ አንባቢ ስኬታማ መሆንን አጥብቆ ይሻ እንደሆነ ለዚህ የናፖሊዮን ሂል መፅሃፍ ትኩረት ሊሰጥ ይገባል፡፡ በዚህ መፅሃፍ ውስጥ የተብራሩት የስኬት መርሆዎች አንባቢ እንዴት ሊረዳቸውና በህይወቱ ውስጥ ተግባራዊ ሊያደርጋቸው እንደሚችል የሚጠቁሙ ጭምር ናቸው” ብሏል፡፡
17ቱ የስኬት መርሆዎች በሚል ከተገለፁት ውስጥ የዓላማ ቁርጠኝነትን ማዳበር፣ ውጤታማ ህብረት መፍጠር፣ አስደሳች ስብዕናን መገንባት፣ በትክክል ማሰብ ወዘተ የሚሉት ይገኙበታል፡፡ በ172 ገፆች የተቀነበበው መፅሃፉ፤ በ18 ምዕራፎች የተከፋፈለ ሲሆን በ39 ብር ከ45 እየተሸጠ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 8802 times