Saturday, 19 October 2013 12:46

“የተወጠረ ገመድ” የሥዕል አውደርእይ ዛሬ ይከፈታል “የኢትዮጵያ ባሕላዊ ሥዕል ኤግዚብሽን ተከፈተ

Written by  መልካሙ ተክሌ
Rate this item
(0 votes)

በሠዓሊ ኤልያስ ሥሜ የተዘጋጁ የሥዕል ሥራዎች የሚቀርቡበት “የተወጠረ ገመድ” የሥዕል ዐውደርእይ ዛሬ በብሪቲሽ ካውንስል የሚከፈት ሲሆን አውደርዕዩ በጎተ ኢንስቲቲዩት፣ በአሊያንስ ኢትዮፍራንሴና በጣሊያን የባሕል ተቋም እንደሚቀርብም ታውቋል። የስዕል አውደርዕዩ በመስከረም አሰግድ ኩሬተርነት የሚቀርብ ነው፡፡ ሰዓሊ ኤልያስ ሥሜ ካሁን ቀደም በግሉ ዘጠኝ ዐውደርእዮች በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ያቀረበ ሲሆን ከሌሎች ሠዐሊያን ጋር ደግሞ ስድስት ዐውደርእዮች አቅርቧል፡፡
በሌላም በኩል “የኢትዮጵያ ባሕላዊ የሥዕል ኤግዚብሽን” ከትናንት በስቲያ በላፍቶ አርት ጋለሪ ተከፍቶ መታየት እንደጀመረ ጋለሪው አስታወቀ። ሳር ቤት ብስራተ ገብርኤል ቤተክርስትያን አካባቢ የተከፈተው ዐውደርእይ፤ አስር ሠዐሊያንን ያሳተፈ ሲሆን እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2006 ዓ.ም ለሕዝብ ክፍት ሆኖ ይቆያል።

Read 798 times