Monday, 25 November 2013 11:06

የመዝገቡ ተሰማ፣ “ንግሥ” ስዕሎች ላይ ውይይት ይካሄዳል

Written by  መልካሙ ተክሌ
Rate this item
(1 Vote)

ባለፈው ሳምንት “ንግሥ” በሚል ርዕስ የተከፈተው የመዝገቡ ተሰማ የስዕል ኤግዚቢሽን ከበርካታ ተመልካቾች እና ሰዓሊያን አድናቆትንና ምስጋናን ያተረፈ ሲሆን፣ በሚቀጥለው አርብ ውይይት ይካሄድበታል ተብሏል፡፡ በ“ሮማንቲክ ሪያሊዝም” ዘይቤ ትላልቅ ስዕሎችን በመስራት የሚታወቀው መዝገቡ ተሰማ፣ 5 ሜትር በ2 ሜትር ስፋት ያለው “ንግሥ” የተሰኘ ስዕልን ጨምሮ 15 አዳዲስ ስዕሎችን ለእይታ አቅርቧል፡፡ በቀለም አዋቂነቱ፣ በምስል ቅንብር ጥበበኛነቱ እና በምጡቅ ክህሎቱ የሚደነቀው መዝገቡ ተሰማ፤ የስዕልን የ “3D” ባህርይ አጉልቶ ለማውጣት አዳዲስ ስልቶችን ተጠቅሟል፡፡
በስዕሎቹ ላይ በሚቀጥለው አርብ በ8 ሰዓት ውይይት የሚካሄደው፤ እዚያው የስዕል አውደ ርዕይ በሚታይበት ብሔራዊ ሙዚየም ውስጥ ነው፡፡ መዝገቡ ተሰማ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የስነጥበብ አስተማሪ እንደሆነ ይታወቃል፡፡  

Read 1462 times