Saturday, 30 November 2013 11:42

“የኢትዮጵያ ኮከብ” ለንባብ በቃ

Written by  መልካሙ ተክሌ
Rate this item
(35 votes)

በአብነት ስሜ የተጻፈው ‘የኢትዮጵያ ኮከብ’ የተሰኘ ኮከብ ቆጠራ (አስትሮሎጂ) መጽሃፍ ባለፈው ሳምንት ለንባብ በቃ፡፡ በአምስት ዋና ዋና ክፍሎችና በአስራ ሰባት ምዕራፎች የተከፋፈለው ‘የኢትዮጵያ ኮከብ’፣ 132 ገጾች ያሉት ሲሆን የግለሰቦችን፣ የአገራትንና የዘመናትን ኮከቦች በተመለከተ ዝርዝር መረጃ ይዟል፡፡ በመጽሃፉ ውስጥ የ500 ታዋቂ ግለሰቦች ኮከቦች ዝርዝር፣ የኢትዮጵያ ኮከብና የ8ኛው ሺህ ዘመን ኮከብ ማብራሪያ የተካተተ ሲሆን እያንዳንዱ አንባቢ ኮከቡን መሰረት በማድረግ የጤና፣ የሙያ ምርጫና የዝንባሌ ምክር በሚያገኝበት መልኩ መሰናዳቱን ፀሃፊው አስታውቋል፡፡ በ50 ብር ለገበያ የቀረበው ‘የኢትዮጵያ ኮከብ’ በየመጽሃፍ መደብሩና በአዟሪዎች እጅ እየተሸጠ ይገኛል፡፡

Read 10363 times