Saturday, 30 November 2013 11:51

“የኢትዮጵያ ኢንተርናሽናል ፊልም ፌስቲቫል” ሰኞ ይጠናቀቃል

Written by  መልካሙ ተክሌ
Rate this item
(2 votes)

በ1997 ዓ.ም ተጀምሮ በየአመቱ እየተካሄደ ያለው “የኢትዮጵያ  ኢንተርናሽናል ፊልም ፌስቲቫል” ስምንተኛ ዝግጅት ባለፈው ሰኞ ምሽት በብሔራዊ ትያትር በሚደረግ የሽልማት ሥነሥርዓት እንደሚጠናቀቅ ሊንኬጅ አርት ሪሶርስ ሴንተር አስታወቀ፡፡ ዝግጅቱን የሚያቀርበው የሊንኬጅ አርት ዋና ሥራ አስኪያጅ አርቲስት ይርጋሸዋ ተሾመ ለአዲስ አድማስ እንደገለፀው፣ በፌስቲቫሉ ማጠናቀቂያ ላይ የተለያዩ ፊልሞች በዘጠኝ የሽልማት ዘርፎች ይሸለማሉ፡፡ በዘንድሮው ፌስቲቫል የተሳተፉት ፊልሞች ካለፈው ሰኞ ጀምሮ በብሔራዊ ትያትር፣ በሲኒማ አምባሳደር፣ በሲኒማ አምፒር፣ በፑሽኪን አዳራሽ እና በጣሊያን የባሕል ማዕከል በቅናሽ ዋጋ እየታዩ ሲሆን የውጭ ሀገራት ፊልሞች በነፃ እየቀረቡ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 3154 times