በደራሲ ገስጥ ተጫኔ እና በቀድሞው የኢትዮጵያ ምድር ጦር ሰራዊት ወታደሮችና ሲቪል ማህበራት ትብብር የተዘጋጀው “የቀድሞው ጦር” የተሰኘ የታሪክ መፅሐፍ ዛሬ ይመረቃል፡፡ የመጽሀፍ ምርቃቱ ዛሬ ጠዋት በዮርዳኖስ ሆቴል የሚከናወን ሲሆን 747 ገፆች እንዳሉትና በ250 ብር ለገበያ እንደቀረበ ደራሲ ገስጥ ተጫኔ ተናግረዋል፡፡ “የቀድሞው ጦር” ለደራሲው ዘጠነኛ መፅሀፋቸው ሲሆን ከዚህ በፊት “የናቅፋው ደብዳቤ”፣ “እናት አገር”፣ “የፍቅር ቃንዛ”፣ “ነበር” ቁጥር አንድና ቁጥር ሁለት፣ የማክዳ ንውዘትና ሌሎችንም ለአንባቢያን አድርሰዋል፡፡