አስራ አራት አንጋፋና አማተር ሰዓሊያን የሚሳተፉበት “ጅማሬ” የተሰኘ የስዕል አውደርዕይ ዛሬ በ11 ሰዓት 30 ሽሮሜዳ ኪዳነምህረት ቤ/ክርስቲያን መንገድ ላይ ታቦት ማደሪያው ፊትለፊት በሚገኘው ሚራጅ ኮፊ ሮስተር ይከፈታል፡፡
የአውደርዕዩ አዘጋጅ አቶ ዮሐንስ አክሊሉ እንደገለፁት፤ አውደርዕዩ እስከ ሐምሌ 5 ቀን 2006 ዓ.ም ለ15 ቀናት ለተመልካች ክፍት ሆኖ የሚቆይ ሲሆን በየሦስት ወሩ የሚዘጋጅ ፕሮግራም እንደሆነም ታውቋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና