በአግዮስ ምትኩ የተደረሰውና “የአደራ መክሊት” የሚል ርዕስ የተሰጠው ትውፊታዊ ልብ-ወለድ መፅሀፍ ሰሞኑን በገበያ ላይ ውሏል፡፡ ባህላዊ መሰረት ያለው ትውፊዊ ልብ-ወለድ መፅሀፉ፤ ከትውልድ ትውልድ ሲተላለፍ ስለመጣ አንድ ጥሩ መንፈስ ስላለው የአደራ መስቀል የሚተርክ ሲሆን መስቀሉ በተለያየ መልኩ ህይወት ባስተሳሰራቸው ገፀ-ባህሪያት ውስጥ መተላለፉ ሲቆም ስለሚገጥሙት ተግዳሮቶች ይዘረዝራል፡፡
በ60 ምዕራፎችና በ265 ገፆች የተመጠነው መፅሀፉ፤ በሊትማን መፅሀፍ መደብር አከፋፋይነት በ69 ብር ከ95 ሳንቲም እየተሸጠ ነው፡፡
Saturday, 19 July 2014 12:44
“የአደራ መክሊት” መፅሀፍ ገበያ ላይ ዋለ
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና