Saturday, 16 August 2014 11:05

የተስፋፅዮን ገ/መስቀል “ጀመረኒ” የትግርኛ አልበም ለአድማጭ ቀረበ

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(1 Vote)

በባህላዊ የማሲንቆ አጨዋወቱ ተወዳጅነትን ያተረፈው አርቲስት ተስፋፅዮን ገ/መስቀል “ጀመረኒ” የተሰኘ አዲስ አልበም ለገበያ አቀረበ፡፡ በ “ዶን ፊልሞች” ፕሮዱዩስ የተደረገው አልበሙ፤ የሰርግ ዘፈንን ጨምሮ 13 ባህላዊ የትግርኛ ዘፈኖችን የያዘ ሲሆን “ዳ’አማት መልቲ ሚዲያ” አሳትሞ እያከፋፈለው ነው፡፡ ድምጻዊው ከዚህ ቀደም “ቆልዑ ገዛና” የተሰኘ ተወዳጅ አልበም ማውጣቱ የሚታወቅ ሲሆን በአሜሪካ፣ በአውሮፓና በመካከለኛው ምስራቅ አገራት ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን አድናቂዎቹ ኮንሰርት ማቅረቡ ታውቋል፡፡

Read 1422 times