Saturday, 23 August 2014 11:56

“ሬጌ ዳንሶል በኢትዮጵያ ቁጥር 1” የሙዚቃ ድግስ ዛሬ ይካሄዳል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)

በአውሮራ ኤቨንትስ ኦርጋናይዘርስ የተዘጋጀው “ሬጌ ዳንሶል ኢን ኢትዮጵያ ቁጥር 1” የሙዚቃ ድግስ ዛሬ  ምሽት ከ12 ሰዓት ጀምሮ በሚሊኒየም አዳራሽ ይካሄዳል፡፡ በሙዚቃ አፍቃሪያን ዘንድ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ድምፃዊ ቢዚ ሲግናል፤ የምሽቱ ኮከብ ሆኖ እንደሚነግስ የአውሮራ ኤቨንትስ ኦርጋናይዘር ሸዊት ቢተው ለአዲስ አድማስ ተናግሯል፡፡ የአሁኑ ኮንሰርት ከወራት በፊት ሊካሄድ ዝግጅቱ ከተጠናቀቀ በኋላ ከቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ኮንሰርት ጋር በመገጣጠሙ አዘጋጆቹ ፕሮግራሙን መሰረዛቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡
“ቀደም ሲል ከሰረዝነው የሙዚቃ ድግስ በላቀ ሁኔታ፣ በድምፅና በላይት ጥሩ አደራጅተነዋል” ያለው ሸዊት ቢተው፤ ናቲ ማን ወጥቶ ሃይሌ ሩትስና ጆኒ ራጋ መካተታቸው ከበፊቱ የሚለይበት አንዱ ጉዳይ ነው” ብሏል፡፡  በዛሬው የሙዚቃ ድግስ ቢዚ ሲግናልን ጨምሮ ሲድኒ ሳልመን፣ ራስ ጃኒ፣ ጃሉድ አወል እና ሃይሌ ሩትስ የሙዚቃ አፍቃሪውን ያዝናናሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የመግቢያ ዋጋ 500 ብር ሲሆን ለVIP 1500 ብር እንደሆነ ታውቋል፡፡ ትኬቶች በኤድናሞል፣ በሸራተን፣ በሚሊኒየም አዳራሽ፣ በሁሉም የቤሉስ ኬክ ቤቶች፣ በማማስ ኪችን፣ በሮሚና በርገርና በክለብ H2O በመሸጥ ላይ ናቸው ተብሏል፡፡

Read 1125 times