ክሪስ ፕሩቲ ስለ ዳግማዊ አፄ ምኒልክ እና እቴጌ ጣይቱ የፃፈችውን መፅሀፍ፣ ውብሸት ስጦታው (ክፉንድላ) ወደ አማርኛ በመመለስ “ዳግማዊ ምኒልክና እቴጌ ጣይቱ” በሚል ርዕስ አሳትሞ ሰሞኑን ለገበያ አውሏል፡፡ መፅሀፉ ስለኢትዮጵያዊያን ስም አወጣጥ፣ የጣይቱ 5ኛ ባል ስለሆኑት የሸዋው ንጉስ አፄ ምኒልክ፣ ስለጣይቱ የእቴጌነት ማዕረግ፣ ከጣልያን ጋር ስለተደረጉት የአምባላጌ፣ የመቀሌና የዓድዋ ጦርነቶችና በርካታ ተያያዥ ታሪኮች ተካተውበታል፡፡ በ18 ምዕራፍ ተከፋፍሎ በ459 ገፅ የተመጠነው መፅሀፉ፤ በ80 ብር ለገበያ የቀረበ ሲሆን ባሳለፍነው ሳምንት ደራሲያን፣ ሃያሲያንና ጋዜጠኞች በተገኙበት በእቴጌ ጣይቱ ሆቴል ተመርቋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና