Monday, 06 October 2014 08:36

“ተምሳሌት” ማክሰኞ ይመረቃል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)

በኢትዮጵያ የሴቶች ማህበራት ቅንጅትና በአጋር ድርጅቶቹ አማካይነት የታተመውና ከ60 በላይ ኢትዮጵያውያን ሴቶችን ታሪክ የያዘው “ተምሳሌት - እጹብ ድንቅ ኢትዮጵያውያን ሴቶች” መጽሃፍ የፊታችን ማክሰኞ አምስት ኪሎ በሚገኘው ብሔራዊ ሙዚየም ይመረቃል፡፡
ከ300 በላይ ገጾች ያሉት መጽሃፉ፣ በአማርኛና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች የተዘጋጀ ሲሆን፣ የአማርኛው ቅጽ 20 ሺህ ኮፒ፣ በመላ አገሪቱ ለሚገኙ ትምህርት ቤቶች፣ የሴቶች ክበባት፣ በሴቶች ዙሪያ ለሚሰሩ ቡድኖችና ድርጅቶች በነጻ ይከፋፈላል ተብሏል፡፡ዋና አዘጋጇም አሜሪካዊቷ ሜሪ ጄን ዋግል ናት፡፡

Read 1192 times