Monday, 06 October 2014 08:38

“ፍካሬ ኢትዮጵያ” ሰኞ በገበያ ላይ ይውላል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)

በደራሲ አብነት ስሜ የተጻፈውና ከዚህ በፊት ለንባብ የበቃው “የኢትዮጵያ ኮከብ” የአስትሮሎጂ መጽሃፍ ቀጣይ ክፍል የሆነው  “ፍካሬ ኢትዮጵያ” ከነገ በስቲያ ጀምሮ በገበያ ላይ ይውላል፡፡ 404 ገጾች ያሉት “ፍካሬ ኢትዮጵያ” የ12ቱ ኮከቦች ሐተታ በ1,200 ስመጥሮች ዝርዝርና በበርካታ ሀገራዊ ምሳሌዎች ታግዞ የቀረበበት ሲሆን፣ ትውፊትን በማኄስ ምርመራ የዐውደ ነገሥት ተወዳሽ እና ተወቃሽ ጐኖችን ይፈትሻል፡፡
መጽሃፉ ልቦለድን በአስትሮሎጂ ማእቀፍ ውስጥ በመተርጐም ሙከራ፣ የ“ፍቅር እስከ መቃብር” የረጅም ልቦለድ መጽሃፍን ገፀ-ባህርያት ኮከብ እና ውክልና የሚቃኝ ሲሆን፣ የታዋቂ ሰዎችን ጉልህ ስብእና በልደት ሰንጠረዥ አማካይነት ተተንትኗል። የኢትዮጵያንና የአስትሮሎጂን፣ የቃላትንና የከዋከብትን፣ የጨረቃንና የሥነ ተዋልዶን ልዩ ተዛምዶም ይዳስሳል፡፡“ፍካሬ ኢትዮጵያ” ከሰኞ ጀምሮ በአዟሪዎችና በመጽሃፍት መደብሮች በ70 ብር ከ80 ሳንቲም ይሸጣል፡፡

Read 2081 times