Monday, 06 October 2014 08:39

“ክሊንገር ሲኒማ” ስራ ጀመረ

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(2 votes)

           በአዲስ አበባ ከተማ ከሚገኙ ሲኒማ ቤቶች በስፋቱ ትልቅ የሆነውን ፐርፎሬትድ ስክሪን ያስገጠመውና በዘመናዊ መልኩ የተደራጀው “ክሊንገር ሲኒማ”፣ አዳዲስ አገረኛ ፊልሞችን በመሳየት አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡
“ክሊንገር ሲኒማ” በተለይ ለአዲስ አድማስ በላከው መግለጫ እንዳለው፣ በአዲስ አበባ ልደታ ኮንዶሚኒየም አካባቢ በሚገኘው መኮንን ቢተው ህንጻ ላይ የተከፈተውና በየዕለቱ በ8፣ በ10 እና በ12 ሰዓት በሶስት ፈረቃ ፊልሞችን ማሳየት የጀመረው ሲኒማ ቤቱ፣ በከተማዋ በስፋቱ ቀዳሚውን ስፍራ የሚይዝ ፐርፎሬትድ ስክሪን ያለው ሲሆን፣ 7.1 ሰራውንድ ሳውንድ ሲስተም የተገጠመለት ነው፡፡ በዘመናዊ መልኩ የተደራጀና የሙቀት መቆጣጠሪያ የተገጠመለት የፊልም አዳራሽ፣ 400 ተመልካቾችን የሚያስተናግዱ ምቹ ወንበሮችና ጥራታቸውን የጠበቁ ተጨማሪ 40 የቪአይፒ ወንበሮችም አሉት፡፡ሲኒማ ቤቱ ለትራንስፖርት ምቹ በሆነ ቦታ ላይ እንደሚገኝ፤ ንጹህና በቂ የእንግዳ ማረፊያ፣ ዘመናዊ ካፌና ሬስቶራንት እንዲሁም አስተማማኝ ጥበቃ ያለው በቂ የመኪና ማቆሚያ እንደተሟላለትም በመግለጫው ተጠቅሷል፡፡

Read 1828 times