በደራሲና አዘጋጅ ሙሉዓለም ጌታቸው ተሰናድቶ፣ በበርሄ ገ/መድህን ፕሮዱዩስ የተደረገው “ሚስቴን ቀሙኝ” የተሰኘ ኮሜዲ የፍቅር ፊልም፤ ነገ በመላ አገሪቱ በሚገኙ የግል ሲኒማ ቤቶች እንደሚመረቅ ፕሮዱዩሰሩ አቶ በርሄ ገ/መድህን ለአዲስ አድማስ ገለፁ፡፡
በሜርሲ መልቲ ሚዲያ ፕሮዳክሽን ለእይታ የሚቀርበውን ይሄን ፊልም ሰርቶ ለማጠናቀቅ አንድ አመት እንደፈጀ የገለፁት ፕሮዱዩሰሩ፤ ከ600 ሺህ ብር በላይ እንደወጣበትና የ1ሰዓት ከ42 ደቂቃ ርዝማኔ እንዳለው ጠቁመዋል፡፡
በፊልሙ ላይ ዮሐንስ ተፈራ (ዳረማኛ)፣ ቃልኪዳን ጥበቡ፣ ሰገን ይፍጠር፣ ካሳሁን ፍሰሃ (ማንዴላ)፣ አስራት ታደሰ፣ ፋንቱ ማንዶዬ፣ እንዳልካቸው ሰበታና ሌሎችም ወጣትና አንጋፋ ተዋንያን ተሳትፈውበታል ተብሏል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና