Monday, 13 October 2014 07:29

“ዳነ” የጉራጊኛ ቪሲዲ ለገበያ ቀረበ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 በጉራጊኛ ዘፈኑና በማራኪ ውዝዋዜው የሚታወቀው የድምፃዊ መላኩ ቢረዳ “ዳነ” የተሰኘ አዲስ የጉራጊኛ ቪሲዲ ሰሞኑን ለገበያ ቀርቧል፡፡ የ14 ዘፈኖችን ቪዲዮ ያካተተው ይኸው ስራ፤ አብዛኞቹ ግጥሞችና ዜማዎች በራሱ በድምፃዊው የተሰሩ ሲሆን ቅንብሩ በዘሪሁን ሳህለማሪያም፣ ያሬድ አስናቀ፣ አሸናፊ ከበደና በሰለሞን ኢብራሂም ነው የተሰራው፡፡
ድምፃዊው በቪሲዲው ውስጥ “ትግርኛ ምት በጉራጊኛ”፣ “አውዳመት አማርኛ በጉራጊኛ ስልት”፣ “ጐንደር በጉራጊኛ”፣ “ሱዳንኛ በጉራጊኛ” እና “ትዝታ በጉራጊኛ” የሚሉትን በማካተት ለየት ባለ ሁኔታ የቀረበ ሲሆን ከዚህ ቀደም “ትዊስት በጉራጊኛ” የተሰኘ ቪሲዲ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ አዲሱ ቪሲዲ በዚያዳ ሪከርድስ ታትሞ እየተከፋፈለ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ድምፃዊ መላኩ ቢረዳ በአሁኑ ሰዓት በዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ ቤት አዳራሽ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡

Read 1756 times