Saturday, 18 October 2014 10:01

‹‹...ጥሩ ቤተሰብ መፍጠር ...ጥሩ አለምን መፍጠር...››

Written by 
Rate this item
(6 votes)

ህጻናትን በፍቅርና በሰላም ማሳደግ የሚቻለው ይበልጡኑ ወላጆች ኃላፊነት የሚሰማቸው እና ጥሩ ምሳሌ ሲሆኑ ነው፡፡ ቤተሰብህን በተሸለ ደረጃ መምራት ማለት አለምን በተሸለ ደረጃ ለመምራት ዝግጁ መሆን ማለት ነው የሚለው የጠበብት ንግግር ተግባራዊ እንዲሆን ሁሉም ልብ ሊለው የሚገባ ነገር ነው፡፡ ወላጅ ልጅን በማስተናገዱ ረገድ እራሱን ሊጠይቅ ከሚገባቸወ ነገሮች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፡፡
* እኔ ወላጅ ከሆንኩኝ ልጄን በትክክል ለመርዳት የሚያስችል በቂ ጊዜ ሊኖረኝ ይገባል? ወይንስ በተጣበበ ጊዜ የማደርገው ነገር ትክክል ነው?
* ለመሆኑ ማድረግ የሚገባኝን እያደረግሁኝ ነውን?
* የትኛው ትምህርት ቤት ባስተምረው ጥሩ ይሆናል?
* ልጄን በሚያዝናና መንገድ እየረዳሁ ነውን? ወይንስ?
* በማደርገው ነገር ውስጤን በትክክል አምነዋለሁኝ? ወይንስ እየተጠራጠርኩ ነው?
የሚሉትንና ሌሎችንም ጥያቄዎች ለራስ በማቅረብ ልጆችን በተገቢው መንገድ ማሳደግ በሁሉም ወላጅ እና ቤተሰብ እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት ላይ የሚጠበቅ ግዴታ ነው፡፡
የኢፌዲሪ ህገመንግስት አንቀፅ 35 ማንኛውም አንድ ህፃን ሊኖረው የሚገቡ መብቶች ብሎ የሚከተሉትን በዝርዝር አስቀምጧል፡-
ሀ) በህይወት የመኖር፣
ለ) ስምና ዜግነት የማግኘት ፣
ሐ) ወላጆቹን ወይም በህግ የማሳደግ መብት ያላቸውን ሰዎች የማወቅና የእነሱንም እንክብካቤ የማግኘት፣
መ) ጉልበቱን ከሚበዘብዙ ልማዶች የመጠበቅ፣በትምህርቱ፣በጤናውና በደህንነቱ ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ስራዎችን እንዲሰራ ያለመገደድ ወይም ከመስራት መጠበቅ፣
ሠ.. በትምህርት ቤቶች ወይም በህፃናት ማሳደጊያ ተቋሞች ውስጥ በአካሉ ከሚፈፀም ወይም ከጭካኔና ኢሰብአዊ ከሆነ ቅጣት ነፃ የመሆን፣ከላይ ከተጠቀሱት ድንጋጌዎች መካከል ተራቁጥር (መ) እንዲሁም (ሠ) ህፃናትን ከተለያዩ አካላዊ ብሎም ስነልቦናዊ ጥቃቶች ለመከላከል ታስቦ የወጣ ነው፤እንደ ኢፌዲሪ ሴቶች ህፃናት እና ወጣቶች ሚንስ..ር አገልለፅ ለጥቃት ተጋላጭ ሆኑ የሚባሉት ህፃናት...
 ‹‹አስፈላጊው እንክብካቤ የማይደረግላቸው እንዲሁም ደህንነታቸው በተለያየ ምክንያት አደጋ ላይ የወደቀና ህገመንግስቱ የደነገገላቸውን መብት መጠቀም ያልቻሉ ህፃናት ናቸው›› children advocacy center የሚለው ሕጻናትን ተንከባክቦ በማሳደግ ረገድ ለዚህ እትም መረጃ ያደረግነው ጽሁፍ ሲጀምር ተከታዮቹን ነጥቦች ይዘረዝራል፡፡
* ከትዳር አጋራችን ጋር የሚኖረን ጥሩ ያልሆነ ግንኙነት፣
* የኢኮኖሚ ችግር ፣
* ከእፅ እና ከአልኮል ጋር የተያያዙ ችግሮች እንዲሁም፣
* በልጅነት ተከስቶ ያለፈ ጥቃት፣
እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት ነጥቦች ወላጆች በልጆቻቸው ላይ ለሚያደርሱት ጥቃት  እንደ መንስኤ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ የቱንም ያህል ልጃቸውን የሚወዱ ወላጆች እን..ን ቢሆኑ እንደችግር ለተጠቀሱት ነጥቦች ትእግስትን ወይንም መቻልን ያጣሉ፡፡ children advocacy center የህፃናት ጥቃትን ለመከለላከል የሚያስችሉ መንገዶች ብሎ ካስቀመጣቸው ሀያ ነጥቦች ውስጥ የተወሰኑትን ሀሳቦች እናስነብባችሁ፡
1/ጥሩ ምሳሌ ወይም አርአያ መሆን፣ ወላጆች ለሁሉም የቤተሰብ አባላት ተገቢውን ቦታ እና ክብር ሊሰጡ ይገባል፤ ልጆችን ትህትና     በተሞላበት መንገድ ማነጋገር ተገቢ ነው፡ አግባብ ያልሆነ ምግባር ሲያሳዩም  እነሱን ሳይሆን ድርጊታቸውን እንዳልወደዱት ከመንገር ባለፈ ፈፅሞ ልጆችን ለመምታት እንዳይሞክሩ ይመከራል፡፡፡
 መምታት ወይም ሌሎች አካላዊ     እርምጃዎችን መውሰድ ልጆች ሀይለኝነትን እንዲማሩ ያደርጋል፡፡ የተሳሳቱ መስሎ ተሰማዎት ይቅርታ ይጠይቁ ይህን በማድግዎ ለልጆ መልካም ባህሪን ያወርሳሉ፡፡
2/ልጅዎን ጓደኛ ማድረግ፣ልብ ይበሉ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ነገሮችን በቁጣ እና በንግግር ብቻ ማለፍ አለመግባባትን ለማቅለል ይረዳል፡፡ ልጆች የወላጆቻቸውን ደስታ እና ጥሩ ፊት ሲያዩ መልካም ምግባር ይኖራቸዋል ስለዚህ ከልጆችዎ ጋር መዝናናትን አሊያም የእግር ጉዞ ማድረግን     ያዘውትሩ፡፡
ይህን መሰል ድርጊቶች ድካምን ለመቀነስ ብሎም ከልጆችዎ ጋር የሚኖርዎትን ግንኙነት ለማጠንከር አይነተኛ መንገድ ነው፡፡
3/ልጆችን ማመስገን ወይም ማበረታታት፣    መጥፎ ቃላት ልጆች ዋጋቢስ እንደሆኑ እንዲሰማቸው ያደርጋል፡፡ ጉዳቱም የእድሜ ልክ ነው፡፡ ስለዚህ በተቻለ መጠን ቀና ይሁኑ፡፡ ምን ያህል በእሱ/በእሷ ደሰተኛ እንደሆኑ እና     በእርስዎ ዘንድ ያላቸውን ቦታ ለልጆቾ አዘውትረው ይንገሯቸው፡፡
4/እርምጃ መውሰድ ወይም ሌሎች እስኪጀምሩ አለመጠበቅ፣በስራ ቦታ እንዲሁም በሌሎች ቦታዎች የህፃናት ጥቃትን በሚመለከት እንቅስቃሴ ማድረግ ይኖርብዎታል፡፡ ስለ ጉዳዩ ይበልጥ ባወቅን ቁጥር ድርጊቱን ለማቆም በይበልጥ እንተጋለን፡፡
5/በጎ ፈቃደኛ መሆን ፣ ጊዜዎን በህፃናት ጥበቃ እንዲሁም ለልጆች ድጋፍ የሚሰጡ ፕሮግራሞችን ለመደገፍ     ያውሉት፡፡
6/ በህፃናት ማቆያ ማእከል ውስጥ ማገልገል፣  ጊዜዎን የተጎዱ እና ጥቃት የደረሰባቸው ህፃናትን ለሚንከባከብ ማእከል የበጎፈቃድ አገልግሎት ለመስጠት ያውሉት ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ህፃናትን ከሚረዱ ማእከላት ጋር     ህብረት በመፍጠር አብረው ይስሩ ፡፡
7/ ስለህፃናት ጥቃት እንዲሁም መከላከያ መንገዶቹ በቂ ግንዛቤ መያዝ፣
8/ ወላጆቻቸውን ላጡ ህፃናት ወላጅ መሆን ፣ ይህን ማድረግ ቀላል አይደለም ነገርግን አንድ ህፃን ደህንነቱ ሲጠበቅ የሚሰማውን ሲያዩ እርካታዎ ከፍያለ ነው፡፡
9/ በሀገር ውስጥ ከሚገኙ እና በህፃናት ደህንነት ላይ ከሚሰሩ አካላት ጋር መስራት፣
10/ የትኞቹ ህፃናት በይበልጥ ለጥቃት ተጋላጭ እንደሆኑ መረዳት፣ ምንም እን..ን የህፃናት ጥቃት ዘር እና ባህል ሳይለይ በሁሉም ህብረተሰብ ክፍል  የሚከሰት ቢሆንም አብዛኛዎቹ አካላዊ ጥቃቶች የሚከሰቱት ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ባለቸው  የህብረተሰብ ክፍሎች ዘንድ ነው፡፡
የአእምሮ ህመም እንዲሁም የአካል ጉዳት ያለባቸው ታዳጊ ህፃናት ደግሞ ለድርጊቱ በይበልጥ ተጋላጭ ናቸው፡፡
11/ የጥቃቱን መገለጫዎች ለይቶ ማወቅ፣
በህፃናት ላይ የሚደርሱ አካላዊ እንዲሁም ፆታዊ ጥቃት መገለጫዎችን ለይቶ ማወቅ     ድርጊቱን ለማወቅ በይበልጥ ይረዳል፡፡
12/  ለልጆች አስፈላጊ የሆኑ ስጦታዎችን አስቀድሞ ማዘጋጀት፣ ይህን ማድረግ ለልጆች ያለንን ፍቅርና እንክብካቤ ከመግለፅ አልፎ እነርሱን ለማሳደግ  ምን ያህ እግጁ እንደሆንን ያሳያል፡፡

Read 6203 times