Monday, 03 November 2014 07:39

የአዳማና ሞጆ ዲጂታል ካርታ እየተሰራ ነው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በኦሮሚያ ክልል የሚገኙትን የአዳማና ሞጆ አካባቢዎች የሚሸፍን የዲጂታል ቶፖግራፊ ካርታ እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ካርታ ስራዎች ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡
ኤጀንሲው ጃይካ ከተባለው ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት ጋር በትብብር የሚሰራው ዲጂታል ቶፖግራፊ ካርታ፣ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ አዲሱ ካርታ ኤጀንሲውን ወደ ዲጂታል የአሰራር ዘዴ እንደሚያሸጋግረው ተጠቁሟል፡፡ የአዳማና ሞጆ አካባቢዎች ለፕሮጀክቱ ስራ የተመረጡት ትላልቅ ፕሮጀክቶችና ሰፋፊ የልማት ስራዎች የሚከናወኑባቸው ስፍራዎች በመሆናቸውና ለአዲስ አበባ ከተማ ያላቸው ቅርበት ስራውን በወቅቱ ለማጠናቀቅ ይረዳል በሚል እንደሆነ ታውቋል፡፡

Read 2891 times