በስንታየሁ ካሣሁን ተደርሶ በምንተስኖት አስቻለው የተዘጋጀው “አዱኛ” ፊልም ነገ ይመረቃል፡፡
ወንጀልን፣ ፍቅርን፣ ክፋትና ደግነትን መሠረት አድርጐ የተሰራው ይኸው ፊልም አንድ ሰዓት ከሃያ ደቂቃ ጊዜን የሚወስድ ሲሆን ፊልሙን ሰርቶ ለማጠናቀቅ አንድ ዓመት ከስድስት ወር ጊዜ እንደወሰደባቸው የፊልሙ አዘጋጅ ለአዲስ አድማስ አስታውቋል፡፡ በፊልሙ ላይ ነብይ አንዋር፣ መሰረት ባጫ፣ ኖአሚን ሳሙኤል፣ ማሩ እንዳለና ሌሎችም ተውነውበታል፡፡ ፊልሙ ነገ በ8፣ በ10 እና በ12 ሰዓት በሁሉም የመንግሥት ሲኒማ ቤቶች ይመረቃል፡፡
Saturday, 29 November 2014 11:48
“አዱኛ” ፊልም ሊመረቅ ነው
Written by ማህሌት ሰለሞን
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና