Saturday, 29 November 2014 11:45

“አመሰግናለሁ” የባህል አውደርዕይ ተከፈተ

Written by  ማህሌት ሰለሞን
Rate this item
(1 Vote)

በሰዓሊ ብሩክ የሺጥላ የተዘጋጀና “አመሰግናለሁ” የሚል ርዕስ የተሰጠው የስዕል አውደርዕይ ትናንት በካፒታል ሆቴል ተከፈተ፡፡
ለአስራ አራት አመታት ሰውነቱን ማንቀሳቀስ ተስኖት በጀርባው ብቻ ተኝቶ የኖረው ሰዓሊ ብሩክ የሺጥላ በዚህ ሁኔታ ላይ ሆኖ የሠራቸውን 40 የቀለም ቅብና ሪልፍ የባህል ሥራዎች በአውደርዕዩ ላይ አቅርቧል፡፡
ሰዓሊው በህመም ላይ በቆየባቸው አመታት ከጐኑ ባለመለየት ድጋፍና እንክብካቤ ያደረጉለትንና ባለፈው ሕዳር ወር በኪቶር ሆስፒታል የተካሄደውን የተሣካ የቀዶ ህክምና ለማድረግ እንዲችል የረዱትን ሁሉ ለማመስገንና ያደረጉለትን እንክብካቤ ለማሰብ አውደ ርዕዩን “አመሰግናለሁ” የሚል ስያሜ እንደሰጠውም ተናግሯል፡፡ ሰዓሊ ብሩክ የሺጥላ ለአስራ አራት አመታት ሰውነቱን ማዘዝ ተስኖት በጀርባው ተኝቶ ከቆየ በኋላ ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር በኪዩር ሆስፒታል በተደረገለት ቀዶ ህክምና ለመቀመጥ መቻሉንና ይህም ታላቅ ደስታ እንደሰጠው ለአዲስ አድማስ ገልጿል፡፡  

Read 2501 times