Saturday, 13 December 2014 11:18

የኢትዮጵያና የፖርቹጋል የ500 ዓመት ግንኙነት በኪነ-ጥበብ ተዘከረ

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(1 Vote)

    በፖርቹጋል ኤምባሲ፣ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና በባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ትብብር የተዘጋጀ የፖርቹጋልንና የኢትዮጵያን የ500 ዓመት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የሚዘክር ኪነ ጥበባዊ ፕሮግራም በብሄራዊ ቴአትር ቀረበ፡፡ ባለፈው ሰኞ ከ6ሰዓት ተኩል ጀምሮ በተካሄደው በዚህ ዝግጅት ላይ በፖርቹጋልና በኢትዮጵያ አርቲስቶች የተለያዩ የጥበብ ስራዎች የቀረቡ ሲሆን የሁለቱም አገራት ተወካዮች ታድመውበታል፡፡ እውቁ ኢትዮጵያዊ የፒያኖ ተጫዋች ግርማ ይፍራሸዋና ፓርቹጋላዊቷ የፒያኖ ባለሙያ ቬራ ኢስትቬዝም የሙዚቃ ስራዎቻቸውን ለታዳሚዎች አቅርበዋል፡፡ በዮሃንስ ተፈራ፣ በእስራኤል መሃሪና በዝናው ደሳለኝ ተፅፎ በተስፋዬ እሸቱ የተዘጋጀው “እንቁ” የተሰኘ ሙዚቃዊ ድራማ ቀርቦ ታዳሚውን ያዝናና ሲሆን የመርድ ታደሰ፣ የቴዎድሮስ ሀጎስ፣ የደረጄ ደምሴና የታምራት ገዛኸኝ የስዕል ስራዎችም ለእይታ ቀርበዋል፡፡

Read 812 times