Saturday, 17 January 2015 10:45

በኢትዮጵያ ኢስላማዊ መንግስት ሊያቋቁሙ ነበር የተባሉት የውጭ ሃገር ዜጎች በእስራት ተቀጡ

Written by  አለማየሁ አንበሴ
Rate this item
(5 votes)

በኢትዮጵያ ኢስላማዊ መንግስት ለማቋቋም በተለያዩ የሽብር ድርጊቶች ውስጥ ተሳታፊ ነበሩ የተባሉ ሶስት የውጭ ሃገር ዜጎች በእስራት ተቀጡ፡፡
“ጀንከታ ሙስሊም” የተሰኘ የጅሃድ አሸባሪ ቡድን በህቡዕ በማቋቋም፣ ኢስላማዊ መንግስት ለመመስረት ሲንቀሳቀሱ ነበር የተባሉት የእንግሊዝ ዜግነት ያላቸው አሊ ሂድሮክና መሃመድ ሸሪፍ እንዲሁም የሶማሊያ ዜግነት ያለው አህመድ መሃመድ ሲሆኑ ግለሰቦቹ አባላት በመመልመል፣ በማደራጀትና ወታደራዊ ስልጠና በመስጠት በኢትዮጵያ ኢስላማዊ መንግስት እንመሰርታለን በሚል ለሽብር ተልዕኮ ሲንቀሳቀሱ እንደነበር የክስ መዝገቡ ያስረዳል፡፡ ሶስቱም ግለሰቦች በዋና ወንጀል ፈፃሚነት የሽብር ድርጊት ለመፈፀም በማቀድ፣ በማሴር፣ በማነሳሳትና ሙከራ በማድረግ በሽብር ተካፋይ ክስ የመሰረተባቸው አቃቤ ህግ በክርክር ሂደቱ አራት ምስክሮችን አቅርቦ ጥፋተኝነታቸውን በበቂ ማስረጃ በማስረዳቱ የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወ/ችሎት ግለሰቦቹ ከ4 ዓመት ከ6 ወር እስከ 4 ዓመት ከ8 ወር በሚደርስ ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ሲል ከትናንት በስቲያ ወስኗል፡፡
በመዝገቡ 1ኛ ተከሳሽ የሆነው አሊ ሃድሮክ በ4 ዓመት ከ6 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጣ  ሲወሰንበት መሃመድ ሸሪፍና አህመድ መሃመድ እያንዳንዳቸው በ4 ዓመት ከ8 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ፍ/ቤቱ ወስኗል፡፡

Read 8065 times