Saturday, 07 February 2015 13:45

ሁለተኛው “የዘመራ ምሽት” ዛሬ በባህር ዳር ይካሄዳል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)

ግጥም በማሲንቆን ጨምሮ የተለያዩ የኪነጥበብ ዝግጅቶች የሚቀርቡበት ሁለተኛው “የዘመራ ምሽት” ዛሬ ማታ በባህር ዳር ካስትል ኩሪፍቱ ዋይን ሃውስ ውስጥ እንደሚካሄድ የፕሮግራሙ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ደምስ አያሌው ለአዲስ አድማስ ገለፁ፡፡ በምሽቱ 13 ግጥሞች በማሲንቆ፣ ክራር፣ ዋሽንትና ከበሮ ታጅበው እንዲሁም ከጀርባ በተዋንያን ደምቀው እንደሚቀርቡ የገለጹት ሥራ አስኪያጁ፤ በየግጥሞቹ መሃልም የጐጃም ባህላዊ ሰርግ ከሆማ ቆረጣ እስከ ብር አምባር በግጥምና በተውኔት እንደሚተወኑ ተናግረዋል፡፡ የኔልሰን ማንዴላ የጀግንነት ህይወት ላይ የሚያጠነጥን ግጥም እንደሚቀርብ ታውቋል፡፡

Read 985 times