ዛሬ የሚከበረውን የፍቅረኞች ቀን (Valentine’s day) የሚዘክር የስዕል አውደ ርዕይ ትላንት በሞርኒንግ ስታር ሞል የተከፈተ ሲሆን በአውደ ርዕዩ የሶስት ሰዓሊያን ስራዎች ለእይታ ቀርበዋል፡፡ ስራዎቻቸውን ያቀረቡት ሰዓሊያን እያንዳንዳቸው የአስር ሺህ ብር ሽልማት የተሰጣቸው ሲሆን በአውደ ርዕዩ ላይ የቀረቡት የሥዕል ሥራዎች ንብረትነታቸው የፕሮግራሙ አዘጋጅ እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡ ለፍቅረኞች ቀን በተዘጋጀው የስዕል አውደ ርዕይ ላይ ለመሳተፍ ከቀረቡ 50 ሠዓሊያን መካከል ሶስቱን የመረጡት ዳኞች እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል፡፡
Saturday, 14 February 2015 15:35
“የፍቅረኞች ቀን” የስዕል አውደ ርዕይ ተከፈተ
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና