የኤርሚያስ መኮንን ድርሰት የሆነውን “አጋምና ቀጋ” የተሰኘ መፅሀፍ ዛሬ ከቀኑ 8፡30 ጀምሮ አራት ኪሎ በሚገኘው ድንቅ ሥራ ህንፃ ላይ እንደሚያስመርቅ “ቡክ ኮርነር” አስታወቀ፡፡ ከምርቃት ሥነስርዓቱ በተጨማሪ የኪነጥበብ ባለሙያዎች፣ ደራሲያንና አንባቢያን በመፅሀፉ ላይ ውይይት ያደርጋሉ ተብሏል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ የ“Tower in the sky” ደራሲ ህይወት ተፈራ እና የ“The Young Crusader” ደራሲ ሰለሞን ኃይለማሪያም በመፃህፍቶቻቸው ላይ የሚፈርሙበት ሥነ-ስርዓት እንደሚካሂድ “ቡክ ኮርነር” በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡
Saturday, 14 February 2015 15:36
ቡክ ኮርነር “አጋምና ቀጋ”ን ዛሬ ያስመርቃል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና