Saturday, 14 February 2015 15:36

ቡክ ኮርነር “አጋምና ቀጋ”ን ዛሬ ያስመርቃል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(1 Vote)

የኤርሚያስ መኮንን ድርሰት የሆነውን “አጋምና ቀጋ” የተሰኘ መፅሀፍ ዛሬ ከቀኑ 8፡30 ጀምሮ አራት ኪሎ በሚገኘው ድንቅ ሥራ ህንፃ ላይ እንደሚያስመርቅ “ቡክ ኮርነር” አስታወቀ፡፡ ከምርቃት ሥነስርዓቱ በተጨማሪ የኪነጥበብ ባለሙያዎች፣ ደራሲያንና አንባቢያን በመፅሀፉ ላይ ውይይት ያደርጋሉ ተብሏል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ የ“Tower in the sky” ደራሲ ህይወት ተፈራ እና የ“The Young Crusader” ደራሲ  ሰለሞን ኃይለማሪያም በመፃህፍቶቻቸው ላይ የሚፈርሙበት ሥነ-ስርዓት እንደሚካሂድ “ቡክ ኮርነር” በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡

Read 1354 times