Saturday, 14 February 2015 15:51

30ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኮትዲቯር ሆነ

Written by  ግሩም ሠይፉ
Rate this item
(0 votes)

ለ31ኛው ግን የአዘጋጅም ፍንጭ  የለም
30ኛው አፍሪካ ዋንጫ በተሳካ ሁኔታ መካሄዱን የተለያዩ ዘገባዎች እየገለፁ ሲሆን፤ ለሚቀጥለው 31ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አዘጋጅ አገር እስካሁን አለመታወቁ አሳሳቢ እንደሆነ እየተነገረ ይገኛል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ፕሬዝዳንት የሆኑት ደቡብ አፍሪካዊቷ ዶክተር ናኮሶዛ ሲያማኒ ዙማ የኢቦላ ስጋትን ድል በማድረግ በተሳካ ሁኔታ የአፍሪካ ዋንጫ መዘጋጀቱን ጠቅሰው ኢኳቶርያል ጊኒ እና የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ኦብያንግ ኑጉዌማ እንዲሁም የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን ውድድሩ የአህጉሪቱን አንድነት እና ሉዓላዊነት በማንፀባረቅ ለተጫወተው ሚና በአድናቆት አመስግነዋል፡፡ በአፍሪካ ዋንጫው የኮትዲቯር ብሄራዊ ቡድን በታሪክ ለሁለተኛ ጊዜ ሻምፒዮን ሆኗል፡፡ የብሄራዊ ቡድኑ ዋና አሰልጣኝ ፈረንሳዊው ሄርቬ ሬናርድ  የአፍሪካ ዋንጫ ከሁለት የተለያዩ ቡድኖች ጋር በአስጨናቂ የመለያ ምቶች ማሸነፋቸውን የማይረሱት ታሪክ እንደሚሆንባቸው ተናግሯል፡፡ከብሄራዊ ቡድን ጋር የዋንጫ ድል ማስመዝገብ ለማመን የሚያስቸግር ደስታ እንደሚሰጥ የተናገረው ደግሞ የኮትዲቯር አምበል የነበረው ያያ ቱሬ ነው፡፡ ለስምንት ዓመታት በቆየበት የብሄራዊ ቡድን ልምድ ህልሙ ይህን የመሰለ ታላቅ ስኬት ማግኘት እንደነበር  ቱሬ አስታውሷል፡፡ ካፍ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት በአፍሪካ ዋንጫው ኮከቦች ምርጫ ጋና በአራት ሽልማቶች ከፍተኛውን ድርሻ ስትወሰድ የዋንጫው አሸናፊ ኮትዲቯር ደግሞ በውድድሩ ምርጥ ቡድን  7 ተጨዋቾች በማስመረጥ ብልጫ አሳይታለች፡፡
 በተያያዘ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን በ30ኛው የአፍሪካ ዋንጫ መገበደጃ ሰሞን በ2017 እኤአ እና በ2018 እኤአ ለሚደረጉት የአፍሪካ እና የዓለም ዋንጫ ውድድሮች ያለውን ማጣርያ ሂደት ይፋ አድርጓል፡፡ ካፍ እንዳስታወቀው ከ3 ሳምንታት በሃላ በ2017 እኤአ ላይ 31ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያዘጋጅ አገር እንደሚታወቅ ሲሆን ወደዚህ ውድድር ለማለፍ የሚደረገው የምድብ ማጣርያ ድልድልም ይገለፃል፡፡ሞሮኮ በ2017ና በ2019 ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች እንዳትካፈል አግዶ መስተንገዶን አለባ ምክንያት በመሰረዝ 1 ሚሊዮንዶላር ቅጣትና 9 ኪሳራ እንድትከፍል ተወስኖባታል፤ አዘጋጅነቱን ለማግኘት ግብፅ ፤ጋና ፤አልጄርያ፤ኬንያ፤ ዚምባቡዌ ፤ጋቦንና ሱዳን ፍላጎት አላቸው፡፡
ለ31ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ታሪክ ለመጀመርያ ጊዜ ያለቅድመ ማጣርያ ወደ ውድድሩ የሚያልፉ ቡድኖችን ለመለየት የምድብ ማጣርያ ብቻ የሚደረግ ይሆናል፡፡ በምድብ ማጣርያው 52 ብሄራዊ ቡድኖች አራት አገራት በሚደለደሉባቸው 13 ምድቦች ተደልድለው የማለፍ እድላቸውን ይወስናሉ፡፡ ከየምድቦቹ በአንደኛ ደረጃ የሚያጠናቅቁት 13 ቡድኖች፤ ምርጥ ሁለተኛ ደረጃ ያገኙ ሁለት ቡድኖች ይሳተፋሉ፡፡ በማጣርያው እንዲሳተፍ የሚገደደው አዘጋጅ አገር   በማጣርያው በመሳተፍ የሚያገኘው ውጤት በወዳጅነት ጨዋታ ይለካበታል፡፡
በሌላ በኩል በ2018 እኤአ ራሽያ ለምታስተናግደው 21ኛው ዓለም ዋንጫ በአፍሪካ አህጉር የሚደረገው ማጣርያ 3 የጥሎ ማለፍ ማጣርያዎች እና አንድ የምድብ ውድድርን የሚያካትት ይሆናል፡፡ በአፍሪካ አህጉር ለዓለም ዋንጣው ለማለፍ በሚደረጉት የ3 ዙር የቅድመ ማጣርያ ምእራፎች ስኬታማ የሆኑት 20 ብሄራዊ ቡድኖች እያንዳንዳቸው አራት አገራት በሚገኙባቸው አምስት ምድቦች በመደልደል በምድብ ፉክክር ይኖራቸዋል፡፡ ምድቦቹን በመጀሪነት የሚያጠናቅቁት አምስት ብሄራዊ ቡድኖች በ21ኛው የዓለም ዋንጫ የአፍሪካ ተወካዮች ይሆናሉ፡፡
በ30ኛው አፍሪካ ዋንጫ
ኮከብ ተጨዋችና ምርጥ ጎል - ክርስትያን አትሱ ጋና
ኮከብ ግብ አግቢ -አንድሬ አየው ፔሌ ከጋና በ3 ጎሎች 2 ጎል የሆኑ ኳሶችን በማቀበል
ኮከብ ግብ ጠባቂ- ሲልቭያን ጎቦሁ ከኮትዲቯር
ኮከብ ስፖርታዊ ጨዋነት -የዲሞክትራቲክ ኮንጎ ቡድን
ምርጥ ቡድን
ግብ ጠባቂ
ሲልቪያን ጎቦሁ ከኮትዲቯር
ተከላካዮች
ሰርጂዬ ኦርዬ ከኮትዲቯር፤ አሪሰን አፉል ከጋና፤ አቢብ ኮሎ ቱሬ ከኮትዲቯር
አማካዮች
አንድሬ አየው ፔሌ ከጋና፤ ያያ ቱሬ ከኮትዲቯር፤ ማክስ አሌያን ጋርዴል ከኮትዲቯር፤ ያኒክ ቦላሴ ከዲሪኮንጎ፤ ጀርቪንሆ ከኮትዲቯር
አጥቂዎች
ክርስትያን አትሱ ከጋና እና ዊልፍሬድ ከኮትዲቯር


Read 1663 times