Saturday, 21 February 2015 13:46

“ትግል አይቆምም” መፅሐፍ ለንባብ በቃ

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(2 votes)

    በሻለቃ ዮሴፍ ያዘው የተጻፈው “ትግል አይቆምም” የተሰኘ የውትድርና መፅሐፍ ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡  ደራሲው ከንጉስ ኃይለሥላሴ እስከ ደርግ ድረስ ያለፉበትን ዘመን ለመፃፍ ያነሳሳቸው ሁለት ምክንያቶች እንደሆኑ ይናገራሉ። አንደኛው፤ከ1966 ጀምሮ እስከ ደርግ መፈጠርና መቋቋም ድረስ የነበረው ትግል  ወጥነት የሌለውና ሁሉም ስለ ራሱ የሚናገርበት በመሆኑ፣ የራሳቸውን የትግል ሂደት በመግለፅ ለታሪክ አስተዋፅኦ ለማድረግ ሲሆን ሁለተኛው ምክንያታቸው፤የተጓዙበት ረጅም የትግል ዘመን ለአሁኑና ለመጪው ትውልድ ትምህርት እንዲሆን በማሰብ ነው ብለዋል፡፡ በሰባት ምዕራፎች የተከፋፈለውና በ285 ገፆች የተቀነበበው መፅሀፉ፤ የሻለቃ ዮሴፍን የትግል ተሳትፎ፣ ገጠመኞችና ትዝታዎች ያካተተ ሲሆን ለአገር ውስጥ በ60 ብር ከ90 ሳንቲም፣ ለውጭ አገር በ25 ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡

Read 2433 times