Monday, 09 March 2015 11:22

“አዲስ አድማስ መስዋዕትነት የከፈለ ጋዜጣ ነው”

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

“አዲስ አድማስ መስዋዕትነት የከፈለ ጋዜጣ ነው”
ዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማርያም
(የአለማቀፍ የህግ ባለሙያና ፖለቲከኛ)
     አዲስ አድማስ እንደሌሎቹ ጋዜጦች በፕሬሱ እንቅስቃሴ ውስጥ መስዋዕትነት የከፈለ፣ ለእውነትና ለሃቅ የታገለ ጋዜጣ አድርጌ ነው የማየው፡፡ እርግጥ እንደ ሌሎቹ የመዘጋት እድል አልገጠመውም፡፡ እንደሚታወቀው አሁን በእስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሣለኝ ያዘጋጃቸው የነበሩ ጋዜጦች በሙሉ ተዘግተዋል፡፡
አዲስ አድማስ ጋዜጣም ምናልባት አስቸጋሪ በሆነ ሁኔታ ውስጥ በቀጭን ክር እየተራመደ ዘልቋል ብዬ አስባለሁ፡፡
ለወደፊትም እንደሚዘልቅ ተስፋ አደርጋለሁ። እስካሁን ድረስ ለመዝለቁም የአዘጋጆቹ ጥበብና ብልህነት ነው እንጂ አፈና ሳይደርስበት ቀርቶ አይደለም፡፡
ለወደፊትም ቢሆን አሁን በያዘው ጥበበኛ አካሄድ ቢቀጥል መልካም ነው፤ ባልሆነ መንገድ ሄዶ መዘጋቱ ለሀገርም ጉዳት ነው፡፡
በተቻለ መጠን የሚዘጋበት ደረጃ እንዳይደርስ በጥንቃቄና በአስተዋይነት ቢጓዝ የበለጠ አስተዋጽኦ ይኖረዋል፡፡ ይሄኛው ጥሩ መንገድ ይመስለኛል፡፡  


Read 3407 times