ጥላሁን ጉግሣ
(የቴያትርና የፊልም ደራሲ፣ ዳይሬክተር፣
ተዋናይና የማስታወቂያ ባለሙያ)
አዲስ አድማስ ጥሩ ጋዜጣ መሆኑን አውቃለሁ፡፡ ጥሩነቱ በቀለሙ ወይንም በወረቀቱ አይደለም፤ በይዘቱ ነው፤ በሚሰጣቸው መረጃዎች፡፡ በአምዶቹ አስተማሪነትና አዝናኝነት ነው፡፡ መረጃዎቹ የጋዜጠኞቹን መረጃ የመፈልፈል ብቃት የሚመሰክሩ ናቸው። አምዶቹ የተለያዩ ሰዎችን የህይወት ተሞክሮና ልምድ የምንማርባቸው ናቸው፡፡ ላለፉት 15 ዓመታት በጥንካሬ ለመቆየታችሁም ሚስጥሩ ይኸው ነው፡፡ ለወደፊቱም በዚሁ እንድትቀጥሉና የተሻሉ ስራዎችን እንድታስነብቡን እመኛለሁ፡፡
Published in
ዜና