Tuesday, 21 April 2015 07:59

“ምስያጥ” የተሰኘ የሞሎች ዳይሬክተሪ ተዘጋጀ

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(1 Vote)

የህንፃ ውስጥ የገበያ ማዕከሎችን ዝርዝር የሚያስቃኝ “ምስያጥ” የተሰኘ የመጀመሪያው የሞሎች ዳይሬክተሪ ወጣ፡፡ በሪዶን የህትመትና የማስታወቂያ ሥራ ድርጅት የተዘጋጀው የሞሎች ዳይሬክተሪው፤ በታወቁ ሆቴሎች፣ ሀይፐር ማርኬቶች፣ ሱፐር ማርኬቶች፣ ቴአትር ቤቶችና የጉዞ ወኪሎች ውስጥ በ20 ብር ይሸጣል ተብሏል። የሞሎቹ ማውጫ ሰዎች የሚፈልጉትን የትኛውንም አይነት ግብይት ከሞሎች በቀላሉ ለመገብየት መረጃ በመስጠት ድካምን እንደሚያቀል የሪዶን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሃይማኖት ፍስሃ ገልፀዋል፡፡

Read 1072 times