Saturday, 02 May 2015 12:11

የህፃናት የንባብና የትምህርታዊ ጨዋታ ቀን በትሮፒካል ጋርደን ይደረጋል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ማልድ የትምህርት ድጋፍ ኃ.የተ.የግ.ማ ባቀራረቡ የተለየ የልጆችን የንባብን ባህል የሚያዳብር፣ ከመጽሐፍ ጋር የተያያዘ የወላጆች ቀን “Book and fun Kids day” /የህፃናት የንባብና የትምህርታዊ ጨዋታ ቀን/ የፊታችን ማክሰኞ በትሮፒካል ጋርደን መናፈሻ ከ4-11 ሰዓት ድረስ ማዘጋጀቱን ገለፁ፡፡
ከ4-14 ዓመት ላሉ ልጆች በተዘጋጀው በዚህ የልጆች ቀን፤ ወላጆች አስተማሪዎች እንዲሁም ትላልቆች ለልጆች መጽሐፍት ያነባሉ፡፡ ጸሐፊያን በዚሁ ቀን መጽሐፍ የማሳተምን ሂደት ለልጆች ያስረዳሉ፣ የተለያዩ ጨዋታዎችም ይኖራሉ፡፡ ማልድ በ21ኛው ክ/ዘመን ልጆች ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ በሚደረገው ጥረት ውስጥ ወላጆች ልጆቻቸውን እንዴት ማሳደግ እንደሚገባቸው ይመክራል ተብሏል፡፡
ማልድ የትምህርት ድጋፍ ሰጪ አስተማሪዎችን በማሰልጠን፣ እንዲሁም ልጆችን ለክፍለዘመኑ ብቁ እንዲሆኑ የሚያግዙ በጥበብና በፈጠራ የተሞሉ ስልጠናዎችን በመስጠት ይታወቃል፡፡

Read 1268 times