Saturday, 02 May 2015 12:13

“የጆርዳና የምግብ አዘገጃጀት” መፅሐፍ ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(27 votes)

 በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ሰርቪስ (ኢቢኤስ) ቴሌቪዥን “የጆርዳና ኩሽና ሾው”    አዘጋጅ ጆርዳና ከብዶም የተፃፈው “የጆርዳና የምግብ አዘገጃጀት” የተሰኘ መፅሀፍ ሰሞኑን ለገበያ ቀርቦ እየተነበበ ይገኛል፡፡ መፅሐፉ ከመቶ በላይ የውጭ ምግቦች አዘገጃጀትን የያዘ ሲሆን ኢትዮጵያዊያን ከተለመደው የአመጋገብ ስርዓታቸው ወጣ ብለው እንደ ፓስታ፣ ፒዛ ያሉ የውጭ ምግቦችን በኩሽናቸው በቀላሉ አዘጋጅተው መመገብ እንዲችሉ ያግዛል ተብሏል፡፡ በኢቢኤስ ቲቪ “ጆርዳና ኩሽና ሾው” እውቅናን ያተረፈችው ባለሙያዋ፤ቦሌ ሩዋንዳ ኤምባሲ አካባቢ “ጆርዳናስ ኪችን ሬስቶራንት” የተሰኘ ምግብ ቤት ከፍታ የውጭ አገር ምግቦችን እያሰናዳች እንደምትሸጥ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 8044 times