Saturday, 20 June 2015 10:09

ምስጋና - ከታጋይ አብጠው ቤተሰቦች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

     ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ በወጣው የአዲስ አድማስ ዕትም ላይ በብዙዎች የተዘነጋውንና ከህወሓት 10 መስራቾች አንዱ የነበረውን የታጋይ አብጠው ታከለን ታሪክ ጋዜጣችሁ ለህዝብ ለማስተዋወቅ ያደረገውን ጥረት እናደንቃለን፤ምስጋናችንንም  እናቀርባለን፡፡ምንም እንኳን የአባታችን የትግል ታሪክ ተገቢውን ዕውቅና እንዲያገኝ ለሚመለከታቸው የፓርቲና የመንግስት ባለሥልጣናት ለማስታወስ  ከጎንደር አዲስ አበባ በመጣን ጊዜ የሚያነጋግረን አጥተን ብንከፋም፣ ጉዳያችንን ለማስረዳት የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ (ነፍሳቸውን ይማርና) ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ቢሮ በሄድንበት ወቅት በታላቅ ክብር፣ ከመቀመጫቸው
ተነስተው በመቀበል  ስላስተናገዱን ልናመሰግናቸው እንወዳለን፡፡ ይሄም ብቻ አይደለም።  ወይዘሮ
አዜብ “ጉዳያችሁ ጉዳዬ ነው” ብለው ታጋይ አብጠውን በተመለከተ የሚቻለው ሁሉ እንዲደረግ የበኩሌን ያለሰለሰ ጥረት አደርጋለሁ በማለት በእጅጉ አበረታተውናልና በድጋሚ ከልብ እናመሰግናለን፡፡ አባታችን አቶ አብጠው ታከለ፤ ከህውሓት የትግል ጥንስስ ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈችበት 2000 ዓ.ም ድረስ ከኢህአዴግ የትግል መስመር ያልወጣና በያዘው አቋም የፀና እንደነበርም በዚህ አጋጣሚ እንዲታወቅልን እንፈልጋለን፡፡
ቤተሰቦቻቸው 

Read 2095 times