‹‹እውነት!?››
አንድ የገዢው ፓርቲ አባል ‹‹ምርጫ በማሸነፉ›› ደስ ተሰኝቶ ሚስቱ ጋ ደወለ አሉ፡፡
‹‹ሄሎ ማሬ!›› ‹አቤት ውዴ! ‹‹ምርጫውን እኮ አሸነፍኩኝ!›› አለ ደስታ ባመጣው ፈገግታ ታጅቦ፡፡ ‹‹እውነት!?›› እሷም ደስታ የሚያደርጋትን አሳጥቷት ባለማመን ጠየቀች፡፡ ጥያቄዋ ግን ባልን አስቆጣው፤ ‹‹እ!? ምን አልሽ አንቺ!›› ‹‹እውነት አሸነፍክልኝ ወይ?› ነው ያልኩት፡፡›› አሁንም ደስታዋ አላባራም፡፡
‹‹አንቺ ሴት ከፀረ ሰላም ኃይሎች ጋር መዋል ጀመርሽ ማለት ነው!?›› ንዴት የሚያደርገውን እያሳጣው፡፡
‹‹ምን እያልክ ነው ውዴ?›› ግራ ቢገባት ጠየቀች፡፡
‹‹እዚህ ጋ ‹እውነት› የሚለውን ቃል ምን አመጣው!? ‹አሸነፍኩ› ማለት፤ ያው አሸነፍኩ ነው! አይገባሽም እንዴ!››
(ከበኃይሉ ገ/እግዚአብሄር ፌስቡክ)
Published in
ህብረተሰብ