15ኛው የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባው የፊታችን ሰኞ እንደሚጀመር ታወቀ፡፡ በሚቀጥለው ዓመት በህዳር ወር በሚካሄደው የጎዳና ላይ ሩጫ ከሁለት ወር በፊት በማንቸስተር ከተማ የሩጫ ውድድሩን ያቆመው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴም የአገር ውስጥ የመጨረሻ ውድድሩን በማድረግ ስንብት ያደርጋል፡፡ አትሌት ኃይሌ የመጀመርያው የተላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አሸናፊ እንደሆነ ይታወቃል፡፡
700 ያህል የውጭ ሀገር ዜጎች በውድድሩ ተሳታፊ እንደሚሆኑ ይጠበቃል ያለው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በውድድሩ ታሪክ ከፍተኛው የተሳትፎ ብዛት እንደሚሆን አመልክቷል፡፡ የመሮጫ ቲሸርት መሸጫ ዋጋውም ወደ 150 ብር ከፍ ያለ ሲሆን የሜዳሊያና የዋንጫ እንዲሁም ሌሎች ወጪዎች በመጨመራቸው ነው ተብሏል፡፡
በውድደሩ ለመሳተፍ ከሚመዘገቡት ውስጥ የመጀመሪያ 1 ሺህ ተመዝጋቢዎች የመለማመጃ ቲሸርት በነጻ የሚያገኙ ሲሆን አቅም ለሌላቸው ሌሎች 1 ሺህ የሚሆኑ ሰዋችም በነጻ የመወዳዳሪያ ቲሸርት የሚሰጥ መሆኑን አስታውቀዋል። ምዝገባውም በ10 የተለያዩ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ይካሄዳል፡፡
Saturday, 27 June 2015 10:11
በ15ኛው ታላቁ ሩጫ ኃይሌ ይሰናበታል
Written by ግሩም ሠይፉ
Published in
ስፖርት አድማስ