Saturday, 04 July 2015 11:08

“የማንነት አደራ” ረዥም ልብወለድ እየተሸጠ ነው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በደራሲ ገነት አዲሱ የተፃፈው “የማንነት አደራ” የተሰኘ የረዥም ልብወለድ መጽሐፍ ባለፈው እሁድ በራስ አምባ ሆቴል የተመረቀ ሲሆን ከሳምንቱ መጀመሪያ አንስቶ በመሸጥ ላይ እንደሆነ ታውቋል፡፡
“ከዓመታት ጀምሮ በርካታ ሃሳቦች በውስጤ ከወዲያ ወዲህ ሲሉ ኖረዋል፤ እነሆ ዘመናቸው መጥቶ በአምላክ እርዳታ ቃሎች ከጥበብ ጋር እንደመዋደድ ያሉልኝ ሲመስለኝ ዛሬ ሃሳቦቼ ጽሑፍ ሆነው ሊወለዱ ደፈሩ” ብላለች፤ ደራሲዋ በመፅሀፉ መግቢያ ላይ ባሳፈረችው ሃሳብ፡፡
በ376 ገፆች የተቀነበበው መጽሐፉ፤ ለአገር ውስጥ በ94 ብር፣ ለውጭ በ25 ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡ ደራሲዋ በኢንተርናሽናል ቴኳንዶ በአፍሪካ የመጀመሪያውን 4ኛ ዲግሪ ያገኘች የማርሻል አርት አስተማሪ ስትሆን “አላዳንኩሽም” እና “ምርቅዝ በቀል” የተሰኙ ፊልሞች ላይ በመተወንም ትታወቃለች፡፡

Read 1716 times