Saturday, 11 July 2015 13:06

“የህይወቴ ፈርጦች” ተመርቆ ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በዓለማየሁ ማሞ የተፃፈው “የህይወቴ ፈርጦች” የተሰኘ ግለታሪክ ከትላንት በስቲያ በኢትዮጵያ ቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን አዳራሽ ተመርቆ ለንባብ በቃ፡፡
ደራሲው በመግቢያው ላይ መጽሐፉን የፃፈበትን ምክንያት ሲያስረዳ፤ “ልጅነቴን፤ የትምህርት ቤት ውሎዬን ኋላም መርከበኛ፤ የጤና ባለሙያ፤ ጋዜጠኛና ደራሲ ሳለሁ ወይም እያለሁ የሆኑትን ግን አንኳር የመሰሉኝን ነው የመረጥኳቸው፡፡ ካሰብኩት ቆየሁ። በዚህም ላይ በጨዋታ መሃል የተነሱ ፈርጦችን ወዳጆቼ ስለወደዷቸው በወረቀት ላይ እንዳኖራቸው ገፋፍተውኛል፡፡” ብሏል፡፡
መጽሐፉ በዘጠኝ ምዕራፎች ተከፋፍሎ በ268 ገፆች የተቀነበበ ሲሆን ለአገር ውስጥ በ80ብር፣ ለውጭ በ20 ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡ ፀሐፊው አለማየሁ ማሞ ነዋሪነቱ  በአሜሪካ ሜሪላንድ ሲሆን ባለፉት 17 ዓመታት ለጠቅላላ ዕውቀት የሚጠቅሙና ይልቁንም ለነፍስ ዕውቀት የሚበጁ በርካታ መፃህፍትን እንዳዘጋጀ ታውቋል፡፡

Read 1820 times