Saturday, 18 July 2015 11:58

የአንዷለም አራጌ “የሀገር ፍቅር እዳ” ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ከሽብርተኝነት ጋር በተያያዘ የእድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባቸው በማረሚያ ቤት የሚገኙት የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የቀድሞ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አንዷለም አራጌ በማረሚያ ቤት ሆነው ለሁለተኛ ጊዜ የፃፉት “የሀገር ፍቅር ዕዳ” መጽሐፍ ለንባብ በቃ፡፡
አቶ አንዷለም አራጌ ከዚህ ቀደም “ያልተሄደበት መንገድ” የተሰኘ መጽሐፍን ለአንባቢያን ያደረሱ ሲሆን “የሀገር ፍቅር እዳ ከቀሳ ጐንደር እስከ ቃሊቲ አስር ቤት” የተሰኘው አዲሱ መጽሐፋቸው በ32 ምዕራፎች ተከፋፍሎ፣ በ400 ገፆች የቀረበ ነው፡፡ ዋጋው 100 ብር ነው፡፡

Read 2081 times