Saturday, 01 August 2015 14:06

ኢትዮጵያዊው በእስራኤል የመጀመሪያው ከፍተኛ የዩኒቨርሲቲ መምህር ሆኑ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

   በእስራኤል በዶክትሬት ዲግሪ የተመረቁ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ናቸው
    ኢትዮጵያዊው ምሁር ዶ/ር አንበሴ ተፈራ በእስራኤል የመጀመሪያው ከፍተኛ የዩኒቨርሲቲ መምህርና የፋካልቲ አባል በመሆን በቴል አቪቭ ዩኒቨርሲቲ ስራ መጀመራቸውን ጂዊሽ ኒውስ ድረገጽ ሰሞኑን ዘገበ፡፡
ዶ/ር አንበሴ በቴል አቪቭ ዩኒቨርሲቲ የእብራይስጥ ባህል ጥናት የትምህርት ክፍል የሴሜቲክ ቋንቋዎች ከፍተኛ መምህር ሆነው እያስተማሩ እንደሚገኙ የጠቆመው ዘገባው፣ ምሁሩ ከ15 አመታት በፊት የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ሲያገኙም በእስራኤል የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ እንደነበሩ አስታውሷል፡፡
በ1962 የተወለዱት ዶ/ር አንበሴ፤ የመጀመሪያና የሁለተኛ ዲግሪያቸውን በሊንጉስቲክስ በተቀበሉበት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለአምስት አመታት ያህል በመምህርነት ማገልገላቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ እየሩሳሌም ውስጥ ከሚገኘው ሂብሩ ዩኒቨርሲቲ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን መቀበላቸውንና በዩኒቨርሲቲው አማርኛ ቋንቋን ሲያስተምሩ እንደቆዩም አክሎ ገልጿል፡፡  
ዶ/ር አንበሴ፤ ሶስት መጽሃፍትንና ከ20 በላይ ጥናታዊ ጽሁፎችን ለህትመት ያበቁ ሲሆን፣ ከማስተማርና ከጥናትና ምርምር በተጨማሪም ለ13 አመታት ያህል ለእስራኤላውያን የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች አማርኛ ቋንቋን በማስተማርና በትምህርት ሚኒስቴር የአማርኛ ጥናቶች ብሄራዊ ሱፐርቫይዘር ሆነው በማገልገል እንደሚታወቁ ዘገባው ጠቁሟል፡፡

Read 1733 times