Monday, 24 August 2015 10:03

የለዛ ፕሮግራም የኪነ ጥበብ ሽልማት በመስከረም ይካሄዳል

Written by  ማህሌት ኪዳነወልድ
Rate this item
(0 votes)

 በሸገር FM 102.1 የለዛ ፕሮግራም፣ የአድማጮች የዓመቱ ምርጥ ኪነ ጥበባዊ ስራዎችና ጥበበኞች ሽልማት በመጪው መስከረም 20 የሚካሄድ ሲሆን አሸናፊዎች በሂልተን ሆቴል በሚደረግ ሥነ - ስርዓት ይሸለማሉ፡፡ ለ1 ወር ከ15 ቀን በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች በተካሄደው የአድማጮች ምርጫ ለመጨረሻ ውድድር የደረሱት እጩዎች መታወቃቸውን የሽልማቱ አዘጋጅ ጋዜጠኛ ብርሃኑ ድጋፌ ለአዲስ አድማስ ገልጿል፡፡  
ለ5ኛ ጊዜ በሚካሄደው የሽልማት ሥነ - ስርዓት ላይ ከያንያንና የጥበብ ስራዎች በ9 ዘርፎች ተወዳድረው እንደሚሸልሙ ታውቋል፡፡
ጋዜጠኛ ብርሃኑ ድጋፌ እንደተናገረው፤ የሽልማት ሥነ - ሥርዓቱን ጃኖ ባንድን ጨምሮ ሚካኤል በላይነህ ለመጀመሪያ ጊዜ ፒያኖ እየተጫወተ በመዝፈን ያደምቁታል፡፡
በየዘርፉ ለመጨረሻው ውድድር የበቁት የጥበብ ሥራዎችና ከያኒያን ከዚህ በታች ቀርበዋል፡፡
ተዋናይ - የዓመቱ ምርጥ
አዚዛ መሐመድ - ሰኔ 30
ሊዲያ ሞገስ - ላምባ
መሠረት መብራቴ - ሃርየት
ሮማን በፍቃዱ - አዲናስ
ብርቱካን በፍቃዱ - ዘጠኝ ሞት
ሠላም ተስፋዬ - ጥለፈኝ
ሄለን በድሉ - በመንገዴ ላይ
የዓመቱ ምርጥ ተዋናይ
ግሩም ኤርሚያስ - ላምባ
ግሩም ዘነበ - ኃረየት
ሰለሞን ቦጋለ - ስለ እናት ልጅ
መሳይ ግርማ - ፍቅርና ገንዘብ
አለማየሁ ታደሠ - ያነገስከኝ
ሽመልስ አበራ - ሰኔ 30
ሰለሞን ሙሄ - የገጠር ልጅ
የዓመቱ ምርጥ ፊልም
ላምባ
ሰኔ 30
አዲናስ
ሼፉ 2
ኃየረየት
ዘጠኝ ሞት
ፍቅርና ገንዘብ 2
የዓመቱ ምርጥ የሙዚቃ አልበም
ማዲንጎ አፈወርቅ - ስወድላት
አብነት አጎናፍር - አስታራቂ
ዮሴፍ ገብሬ - መቼ ነው
ዳን አድማሱ - ዘበናይ
ፀሐዬ ዮሐንስ - የኔታ
ብሩክታይት ጌታሁን - ማነው ፍፁም
የዓመቱ ምርጥ ኦሪጅናል የፊልም ማጀቢያ ዘፈን
ሀርየት - ፀደኒያ ገ/ማርቆስ
ላምባ - አንተነህ ምናሉ
ያየ ይፍረደው - ማቲያስ ይልማ
ሼፉ 2 - ካሳሁን እሸቱ
ፍቅርና ገንዘብ 2 - ኤልያስ ሁሴን
ዘጠኝ ሞት - ሀይሉ መርጋ
የዓመቱ ምርጥ ነጠላ ዜማ
ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) - በሰባ ደረጃ (ታን ታራራም)
የኛ - ስደት
ዘሪቱ ከበደ - ሰይፍህን አንሳ
ጃኪ ጎሲ - አልሰማም
ጎሳዬ ተስፋዬ - አለቃዬ
አብነት አጎናፍር - Maal Naa Wayaa (አሮምኛ)
መሀሙድ አህመድ - ሀገሬ
ፀደኒያ ገ/ማርቆስ - የፍቅር ግርማ
የሕይወት ዘመን ተሸላሚ
ማሪቱ ለገሰ
አለማየሁ እሸቴ
ባህታ ገ/ህይወት
ዳዊት ይፍሩ
ግርማ በየነ
ግርማ ነጋሽ
ዮሀንስ አፈወርቅ
አዲስ ድምፃዊ
ዳን አድማሱ - ዘበናይ
ሀና ግርማ - እውነት
ብሩክታይት ጌታሁን - ማነው ፍፁም
ራስ ዮሐንስ (ጆኒ) - ሰላምታ
ምርጥ የሙዚቃ ቪዲዮ
ዮሴፍ ገብሬ (ጆሲ) - ሽክ ብለሽ (ፊቸሪንግ ጃሉድ)
አብነት አጎናፍር - አስታራቂ
ማዲንጎ አፈወርቅ - ታንጉት
አብነት አጐናፍር - ማነው ያለው
ቤቲ ጂ - ና ና ደማዬ
ፀሐይ ዮሐንስ - የኔታ
ታምራት ደስታ - ከዛ ሰፈር

Read 3051 times