በተስፋዬ በላይነህ የተፃፈው የታሪክ መጽሐፍ፤ “ትንሣኤ ናፋቂዎች - መልዕክት ወደ ኢትዮጵያ ሰዎች” ይላል፡፡ ባለፈው ሳምንት ለገበያ የቀረበው ይሄ መፅሐፍ፤ በ302 ገፆች የተቀነበበ ሲሆን በሁለት ክፍሎችና በሰባት ምዕራፎች የተዘጋጀ ነው፡፡ ከምዕራፎቹም መካከል “የኢትዮጵያ ታሪክ ሥልጣኔ - እድገት ወይስ ውድቀት?”፣ “የኢትዮጵያ ህዝቦች ታሪክ በአጭር ምልከታ”፣ “ታሪክ በየ33 ዓመት” ፣ “የኢትዮጵያ ታሪክ የውድቀት ምክንያቶች” የሚሉ ርዕሶች ይገኙበታል፡፡
መጽሐፉ ለአገር ውስጥ በ69 ብር፣ ለውጭ በ20 ዶላር እንደሚሸጥ ታውቋል፡፡
ደራሲው ከዚህ ቀደም “የሚንከራተቱ ክዋክብት” የተሰኘ መጽሐፍ አሳትሟል፡፡
Monday, 24 August 2015 10:09
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና