Friday, 11 September 2015 09:34

“የራሴን ሀሳቦች የመፃፍ ዕቅድ አለኝ” አርቲስት ሳምሶን ታደሰ (ቤቢ)

Written by 
Rate this item
(2 votes)

    እግዚአብሔር ይመስገን 2007 ለኔ ስኬታማ ስራዎችን የሰራሁበት ዓመት ነው፡፡ በህብረተሰቡ  ዘንድ ተቀባይነት ያገኙ “ባንቺ የመጣ“ እና #አለም በቃኝ” የተሰኙ ሁለት ፊልሞችን ሰርቻለሁ፡፡ በትወና የተሳተፍኩበት “ሶስት ማዕዘን; የተሰኘው ፊልምም፤ በአሜሪካው የ#ፓንአፍሪካን ፊልም ፌስቲቫል” ላይ ተሸልሟል፡፡ በተጨማሪም በመስከረም ወር ለሚካሄደው African Movie Academic Award/AMMA በምርጥ አክተርነት ዘርፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የታጨሁ ኢትዮጵያዊ የሆንኩትም በዚሁ ዓመት ነው፡፡  እኔ ብዙም የእቅድ ሰው አይደለሁም፡፡ በመጪው ዓመት እግዚአብሄር ከፈቀደ በጭንቅላቴ የሚመላለሱ የራሴ ሀሳቦችን የመፃፍ ዕቅድ አለኝ፡፡ የራሴን ስራዎች ለመስራት እሞክራለሁ፡፡ በቲያትሩ በኩልም “3ኛ አይንን” ጨምሮ ሌሎች የምሰራቸው ስራዎች ይኖራሉ፡፡ በሰለሞን ቦጋለ ተፅፎ ዳይሬክት የተደረገውና በትወና የምሳተፍበት “የራስ መንገድ” የሚለው ፊልምም ለእይታ ይበቃል፡፡ በበጎ አድራጎቱ በኩልም ሰለሞን ቦጋለን ጨምሮ ከሌሎች አርቲስቶች ጋር በመሆን የምንሰራቸው ስራዎች ይኖራሉ፡፡

Read 3892 times