Friday, 11 September 2015 09:57

ብሔራዊ ቴያትር ለበዓሉ የሙዚቃ ትርኢት ያቀርባል

Written by  ማህሌት ኪዳነወልድ
Rate this item
(0 votes)

     የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴያትር የአዲስ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ ከጳጉሜ 1 ጀምሮ ሲያቀርብ የነበረውን የሙዚቃ ዝግጅት፣ እስከ መስከረም መጨረሻ እንደሚዘልቅበት የታወቀ ሲሆን በአቶ አክሊሉ ዘውዴ ኮንዳክት የተደረጉ ባህላዊና ዘመናዊ ሙዚቃዎች ይቀርባሉ ተብሏል፡፡ ዛሬ በዋዜማው የተለያዩ የሙዚቃ ትርኢቶች ከምሽቱ 12 ሰዓት እስከ 3 ሰዓት ይቀርባሉ፡፡ድምፃዊ አረጋኸኝ ወራሽና ግርማ ተፈራን ጨምሮ የተለያዩ ተጋባዥ ድምፃውያን በፕሮግራሙ ላይ ያቀነቅናሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በፕሮፌሰር አበበ አሻግሬ ተፅፎ በሳሙኤል ተስፋዬ የተዘጋጀው አጭር ድራማም የፕሮግራሙ አካል ነው፡፡ የሙዚቃ ትርኢቱን ዛሬ ከምሽቱ 12 ሰዓት እስከ 3 ሰዓት እንዲሁም ነገ ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ በ40 ብር መታደም ይቻላል ተብሏል፡፡

Read 888 times