Saturday, 19 September 2015 09:22

መሰረታዊ የስነ-ፅሁፍ ስልጠና የወሰዱ ዛሬ እውቅና ያገኛሉ

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)

  የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር፤ከመላው አገሪቱ አሰባስቦ በመሰረታዊ የስነ ፅሁፍ ትምህርት ላሰለጠናቸው ሰልጣኞች ዛሬ ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በቤተመዘክር እውቅና እንደሚሰጥ አስታወቀ፡፡ ማህበሩ ዘንድሮ ለሶስተኛ ዙር ከሐምሌ 6 ቀን እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2007 ዓ.ም ለሁለት ወራት  መሰረታዊ የሥነ ፅሁፍ ስልጠና ሲሰጥ መቆየቱን ለማወቅ ተችሏል፡፡ የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር ከተቋቋመበት መሰረታዊ አላማዎች አንዱ ተተኪ ፀሀፍትን ማፍራት ሲሆን በየዓመቱ ከመላው አገሪቱ አሰባስቦ ስልጠና መስጠቱም የተነሳበትን አላማ ለማሳካት እንደሆነ ተገልጿል፡፡  

Read 1273 times