“የተያዙና ያልተያዙ ቦታዎች” በሚል ርዕስ የተዘጋጀው 17ኛው ዙር የስዕል ትርኢት የፊታችን አርብ ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ እንደሚከፈት ጋለሪያ ቶሞካ አስታወቀ፡፡ የወጣቱ ሰዓሊ ቃልኪዳን ሾቤ ስራዎች የሚቀርቡበት የስዕል ትርኢቱ፤ለቀጣዩ ሁለት ወራት ለተመልካች ክፍት ሆኖ እንደሚቆይም የጋለሪያ ቶሞካ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ጋዜጠኛ ነብዩ ግርማ ገልጿል፡፡ ሳርቤት ካናዳ ኤምባሲ ፊት ለፊት በሚገኘው ጋለሪያ ቶሞካ ለእይታ የሚቀርቡት የሰዓሊው ሥራዎች፤ትርኢቱ በተከፈተ በወሩ የስዕል አፍቃሪዎች፣ሰዓሊያንና ተጋባዥ እንግዶች በታደሙበት ውይይት እንደሚደረግባቸውም ተጠቁሟል፡፡
Saturday, 19 September 2015 09:23
“የተያዙና ያልተያዙ ቦታዎች” የስዕል ትርኢት ይከፈታል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና