Saturday, 19 September 2015 09:26

“የልጆች ባህሪያትና የአስተዳደግ ጥበብ” ለንባብ በቃ

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(3 votes)

     በልጆች ባህሪያትና የአስተዳደግ ጥበብ ላይ ትኩረት አድርጐ የተዘጋጀውና በወንደሰን ተሾመ መኩሪያ የተፃፈው “የልጆች ባህሪያትና የአስተዳደግ ጥበብ” መጽሐፍ ባሳለፍነው ሳምንት ገበያ ላይ ውሏል፡፡ ለወላጆች፣ ለአሳዳጊዎች፣ ለመምህራን፣ ለአሰልጣኞች፣ ለአማካሪዎች እንዲሁም በልጆች ዙሪያ ለሚሰሩ ግለሰቦችና ተቋማት ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው የተባለው መጽሐፉ፤ በልጆች አስተዳደግ አቀራረቦችና መሰረታዊ ዘይቤዎች፣ በልጆች ስብዕና ቀረፃ መሰረታዊ ክህሎቶች፣ ልጆች በተለያዩ የእድሜ ክልል ስለሚኖራቸው እድገትና የወላጆች ሚና በሚሉና በሌሎች በርካታ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ዳሰሳ አድርጓል፡፡
በ13 ምዕራፎች የተከፋፈለውና በ398 ገፆች የተመጠነው መጽሐፉ፤ ለአገር ውስጥ በ120 ብር፣ ለውጭ በ20 ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡

Read 1804 times